-->
የአገልግሎት ማውጫ📑 ⬇️
ሰላም የሀገሬ ነጋዴዎች ባለጉዳዮች! 🇪🇹
ከቲክቶክ ለምትመጡ ሙሉ መረጃ እንዲከፍትላቹ ከላይ ... ነክታችሁ Open in Browser በሉ | ወይም Google ላይ "Heena Digital Market" ብላችሁ ፈልጉ
እንኳን ደህና መጡ!

HEENA DIGITAL MARKET

የኢትዮጵያ ነጋዴዎችና ባለጉዳዮች በአንድ ቦታ!!!

🏢 አዲስ ንግድ ፍቃደ ለማውጣት

አዲስ ንግድ ፍቃደ ለማውጣት

🏢 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር1395/2017

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር1395/2017

🏢 ውልና ማስረጃ ቀጠሬ ለማስያዝ

ውልና ማስረጃ ቀጠሬ ለማስያዝ

🏢 መንገድ ትራንስፖርት ጉዳይ አስፈፃሚ አገደ

መንገድ ትራንስፖርት ጉዳይ አስፈፃሚ አገደ

🏫

QR ደረሰኝ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ


⚖️ ከደረሰኝ ጋር የተያያዙ ወንጀሎችና ቅጣቶች ማንኛውም ታክስ ከፋይ
 ደረሰኝን በተመለከተ ስህተት ቢፈጽም የሚከተሉት ከባድ ቅጣቶች ይጠብቁታል። 
 1. ያለ ደረሰኝ ግብይት ማከናወን የገንዘብ ቅጣት፦ ከብር 25,000 እስከ ብር 50,000። 
 የእስራት ቅጣት፦ ከ 3 እስከ 5 ዓመት ጽኑ እስራት።
 2. የሽያጭ ዋጋን አሳንሶ መመዝገብ (በደረሰኝ ኮፒዎች ላይ የተለያየ ዋጋ መጻፍ)
 የገንዘብ ቅጣት፦ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር)።
 የእስራት ቅጣት፦ ከ 5 እስከ 7 ዓመት ጽኑ እስራት።
 3. ከፍተኛ የሽያጭ ዋጋ ማጭበርበር (ትክክለኛው ዋጋ ከብር 100,000 በላይ ከሆነ)
 የገንዘብ ቅጣት፦ በደረሰኙ ላይ የተጻፈው ከፍተኛው የገንዘብ መጠን። 
 የእስራት ቅጣት፦ ከ 7 እስከ 10 ዓመት ጽኑ እስራት።

አማራጭ ነው አማራጭ አነስተኛ ግብር
 (Alternative Minimum Tax) ማንኛውም ድርጅት ወይም ሰው በንግድ ሥራው ካገኘው ትርፍ ላይ የሚከፍለው ግብር፣ ዓመታዊ ጠቅላላ ገቢው 2.5% በታች ከሆነ "አማራጭ አነስተኛ ግብር" መክፈል ይኖርበታል።
 📝 የማስከፈያ መጣኔዎች (2.5%)፡ ለድርጅቶች፦
 ከዓመታዊ ጠቅላላ ገቢው 2.5%። 
ለባንኮች፦ ከባንክ ሥራ ከተገኘ የተጣራ ገቢ 2.5%።
 ለኢንሹራንስ፦ ከጠቅላላ አረቦን (Premium) 2.5%። 
ለኮሚሽን ወኪሎች፦ ከኮሚሽን ገቢያቸው 2.5%። 
 💡 ማወቅ ያለብዎት ነጥቦች፡ ተቀናሽነት፦ 
 ኪሳራ ላስመዘገቡ የሚከፈለው ግብር፣ 
በንግድ ትርፍ ግብር ላይ እስከ 5 ዓመት ድረስ ተቀናሽ ሊደረግ ይችላል።
 ከግብር ነፃ የሆኑ፦ በኪሳራ ምክንያት በመፍረስ ላይ ያሉ ወይም በእዳ ማሸጋሸግ ላይ ያሉ ድርጅቶች ከዚህ ግብር ነፃ ናቸው።
 የግብር እፎይታ፦ የኢንቨስትመንት ግብር እፎይታ (Tax Holiday) ያላቸው ድርጅቶች ላይም ይሄ መመሪያ ተፈጻሚ ይሆናል ።
 ትርጉም፦ "ዓመታዊ ጠቅላላ ገቢ" ማለት በግብር ዓመቱ ከዕቃ ሽያጭና ከአገልግሎት የተገኘ ጠቅላላ ገቢ ነው።


  • የቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት አፈጻጸም መመሪያ (witholding tax)

  • አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል በተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። (witholding tax)

  • በአዋጅ መሰረት :- ግዥ ላይ፦ ከአንድ ግዥ ክፍያ መጠን 20,000 ብር በላይ ሲሆን 3% ቅድመ ግብር ተቀንሶ መያዝ አለበት።
    በአገልግሎት ግዥ ላይ፦ ከአንድ ክፍያ መጠን 10,000 ብር በላይ ሲሆን 3% ቅድመ ግብር ተቀንሶ መሰብሰብ አለበት።


  • የ2018 ዓ.ም የቅድመ ግብር ክፍያ የጊዜ ሰሌዳ በአዲሱ የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት፣ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን በየሦስት ወሩ 25% አስቀድመው መክፈል ይኖርባቸዋል። 

    መነሻውም ባለፈው ዓመት የከፈሉት ግብር ነው። 


     1. የሂሳብ ሪፖርት እስከ ጥቅምት 30 የሚያቀርቡ (ደረጃ "ሀ") እነዚህ ግብር ከፋዮች በ2018 ዓ.ም ክፍያ የሚጀምሩት ከየካቲት 1 እስከ 30 ባለው ጊዜ ነው።

     የክፍያ ዙርየሦስት ወሩ ጊዜየማሳወቂያ እና የመክፈያ ጊዜ 

     1ኛ ዙር ከሕዳር እስከ ጥር ከየካቲት 1 – የካቲት 30

     2ኛ ዙር ከየካቲት እስከ ሚያዝያ ከግንቦት 1 – ግንቦት 30 

    3ኛ ዙርከግንቦት እስከ ሐምሌከነሐሴ 1 – ነሐሴ 30 መጨረሻ ቀሪው ክፍያ እስከ ጥቅምት 30

     2. የሂሳብ ሪፖርት እስከ ጥቅምት 30 የሚያቀርቡ (ደረጃ "ሀ") እነዚህ ግብር ከፋዮች በ2018 ዓ.ም ክፍያ የሚጀምሩት ከየካቲት 1 እስከ 30 ባለው ጊዜ ነው።

     የክፍያ ዙርየሦስት ወሩ ጊዜየማሳወቂያ እና የመክፈያ ጊዜ

    1ኛ ዙርከሕዳር እስከ ጥርከየካቲት 1 – የካቲት

     30

    2ኛ ዙርከየካቲት እስከ ሚያዝያከግንቦት 1 – ግንቦት 30

    3ኛ ዙርከግንቦት እስከ ሐምሌከነሐሴ 1 – ነሐሴ 30መጨረሻቀሪው ክፍያእስከ ጥቅምት 30 ማሳሰቢያ

     -ቅድሚያ የከፈሉት ግብር ከዓመታዊ ግብሩ ካነሰ ልዩነቱን ይከፍላሉ፤ ከበለጠ ግን ተመላሽ መጠየቅ ይችላሉ። 

     -በሌላ የጊዜ አቆጣጠር ሪፖርት የሚያቀርቡም፣ ሪፖርት ካቀረቡበት ወር ማግስት ጀምሮ በየሦስት ወሩ መክፈል ይኖርባቸዋል።

    የንግድ ፍቃድ እድሳት በጊዜው ካላደስን ቅጣት ስንት ነው። 
     ከ ጥር 1 እስከ ጥር 30 ብር 2,500.00 
     ከ የካቲት 1 እስከ የካቲት 30 ብር 4,000.00
     ከ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 30 ብር 5,500.00 
     ከ ሚያዚያ 1 እስከ ሚያዚያ 30 ብር 7,000.00  
     ከ ግንቦት 1 እስከ ግንቦት 30 ብር 8,500.00 
     ከ ሰኔ 1 እስከ ሰኔ 30 ብር 10,000.00 
     
     ከሃምሌ 1 ጀምሮ ለሚመጣው 1 አመት 20,000.00
     ከ 1 ዓመት በኋላ ፍቃዱን በአዋጅ ይታገዳል በተጨማሪም ነጋዴው ለ 1 አመት በታገደው የፍቃድ መስጫ መደብ ፍቃድ ማውጣት እንዳይችል ይታገዳል። ማሳሰቢያ አብዛኛውን ጊዜ ነጋዴዎች ንግድ ፍቃድ ለማደስ ወሩ መጨረሻ ላይ ስለሚመጡ ቀድመው በማደስ ፈጣን አገልግሎት ያግኙ!!!

    ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ መክፈያ ጊዜው ውስጥ ታክስ ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ፦ 

     ሀ) ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ)፤ እና 


     ለ) ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ ተጨማሪ 2% (ሁለት በመቶ)፤ ቅጣት ይከፈላል፡፡ 


     ☞ የሚጣለው የቅጣት መጠን ከዋናው የታክስ ዕዳ መብለጥ የለበትም፡፡ 


     መከፈል በማይገባው ታክስ ላይሳይከፈል በዘገየበት የተጣለ ቅጣት ለታክስ ከፋዩ ይመለሳል፡፡ 


     ☞ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት ከተከፋይሂሣብ ላይ ተቀንሶ ከሚከፈል ታክስ ጋር በተገናኘ የሚጣል ቅጣት በሚመለከተው ያልተከፈለ ታክስ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡




    📢 የውጭ አገር ሥራ አገናኝ ኤጀንሲዎች ምዝገባ ጥሪ

    የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአዲሱ አዋጅ መሠረት ኤጀንሲዎች በ3 ቀናት ውስጥ እንዲመዘገቡ አሳስቧል። ምዝገባው በ5 ደረጃዎች የተከፈለ ሲሆን እያንዳንዱ ደረጃ የራሱ ኮታ እና መሥፈርት አለው።

    🏗️ የደረጃዎቹ መሥፈርቶች ባጭሩ፡

    1ኛ ደረጃ፦ 50+ ሠራተኞች፣ 20 ሚሊዮን ብር ካፒታል እና $250,000 ዋስትና።

    2ኛ ደረጃ፦ 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል፣ $200,000 ዋስትና እና እስከ 8 አገራት ፈቃድ።

    3ኛ ደረጃ፦ ለቤት ውስጥ ሥራ ብቻ፣ 10 ሚሊዮን ብር ካፒታል እና $150,000 ዋስትና።

    4ኛ ደረጃ፦ እስከ 4 አገራት ፈቃድ እና $100,000 ዋስትና።

    5ኛ ደረጃ፦ 5 ሚሊዮን ብር ካፒታል፣ $50,000 ዋስትና እና እስከ 2 አገራት ፈቃድ።

    ⚠️ ኤጀንሲዎች ያነሱት ቅሬታ፡
    ኤጀንሲዎቹ የተሰጣቸው 3 ቀናት በጣም አጭር መሆኑንና የዋስትና ገንዘቡ የትና እንዴት ገቢ እንደሚደረግ ግልጽ መመሪያ አለመውጣቱን ገልጸዋል። ይህም ልምድ ያላቸው ኤጀንሲዎች ከሥራ ውጭ ሊሆኑ ይችላሉ የሚል ስጋት ፈጥሯል።

                            የQR ደረሰኝ
    #QR ኮድ ደረሰኝ ልዩ መለያ ኮድ የሌለው ነባሩ የእጅ በእጅ ሽያጭ ደረሰኝ ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንደማይውል ገቢዎች ሚኒስቴር አሳውቋል።

     ሚኒስቴሩ " የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) ያለበት የማንዋል ደረሰኝ ከባለፈው ዓመት ታሕሣሥ ወር ጀምሮ ወደ ሥራ ገብቷል " ሲል አስታውሷል። ነባሩ የእጅ በእጅ ሽያጭ ደረሰኝም ከነገ ጀምሮ ሥራ ላይ እንደማይውል አሳውቋል። 

     በዚህ መሰረትም ከነገ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ልዩ መለያ ኮድ (Unique QR Code) ያለበት የማንዋል ደረሰኝ ብቻ ለአገልግሎት እንደሚውል ገልጿል፡፡ 

    የሕትመት ጥያቄ አቅርበው የታተመላቸውን ደረሰኝ ያልወሰዱ ግብር ከፋዮች ደግሞ በሚከፍሉበት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወይም በየታክስ ማዕከላቸው በመገኘት ደረሰኞቻቸውን እንዲረከቡ አሳስቧል።

     በተመሳሳይ ግብር ከፋዮች እጃቸው ላይየሚገኘውን የቀድሞ ደረሰኝ ለየታክስ ማዕከሎቻቸው በመመለስ የመልቀቂያ ሰነድ መውሰድ እንዳለባቸው አመልክቷል፡፡

     መመሪያውን በማይተገብሩ አካላት ላይ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ርምጃ እንደሚወስድም 

    ለተጨማሪ መረጃ ይቀጥሉ የሚለውን ይጫኑ

    ይቀጥሉ ➡️