-->
የአገልግሎት ማውጫ📑 ⬇️
ሰላም የሀገሬ ነጋዴዎች ባለጉዳዮች! 🇪🇹
ከቲክቶክ ለምትመጡ ሙሉ መረጃ እንዲከፍትላቹ ከላይ ... ነክታችሁ Open in Browser በሉ | ወይም Google ላይ "Heena Digital Market" ብላችሁ ፈልጉ
እንኳን ደህና መጡ!

HEENA DIGITAL MARKET

የኢትዮጵያ ነጋዴዎችና ባለጉዳዮች በአንድ ቦታ!!!

🏢 አዲስ ንግድ ፍቃደ ለማውጣት

አዲስ ንግድ ፍቃደ ለማውጣት

🏢 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር1395/2017

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር1395/2017

🏢 ውልና ማስረጃ ቀጠሬ ለማስያዝ

ውልና ማስረጃ ቀጠሬ ለማስያዝ

🏢 መንገድ ትራንስፖርት ጉዳይ አስፈፃሚ አገደ

መንገድ ትራንስፖርት ጉዳይ አስፈፃሚ አገደ

🏫

QR ደረሰኝ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ

የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን ቅጣት

⚠️ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽንን በወቅቱ አለማሳደስ ቅጣቱ ምንድን ነው?

ለነጋዴዎች የሚሰጥ ወሳኝ የጥንቃቄ መረጃ

የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽንን በሕጉ መሠረት በየዓመቱ አለማሳደስና የቴክኒክ ምርመራ አለማድረግ ከባድ የአስተዳደር ቅጣትና የንግድ መስተጓጎል ያስከትላል። ዝርዝር መመሪያው የሚከተለውን ይመስላል፦

የገንዘብ ቅጣቱንና ዝርዝር እርምጃዎቹን እዚህ ያንብቡ 📖

💵 1. የገንዘብ ቅጣት (የአስተዳደር ቅጣት)፦

ወቅቱን ጠብቆ አለማሳደስ፦ ማሽኑ በየዓመቱ መታደስ (የአገልግሎት ውል መታደስና የቴክኒክ ምርመራ መደረግ) ያለበት ሲሆን፣ ይህንን በወቅቱ ሳያደርጉ ቀርተው ማሽኑ አገልግሎት መስጠት ካቆመ ወይም ፍቃዱ ካለፈ እስከ ብር 25,000 የገንዘብ ቅጣት ሊጣል ይችላል።

ማሽኑ ሳይታደስ ሽያጭ መቀጠል፦ ማሽኑ ሳይታደስ ወይም የቴክኒክ ምርመራ ሳይደረግለት ሽያጭ ማካሄድ እና ደረሰኝ መቁረጥ ተጨማሪ የአሠራር ጥሰት ተደርጎ ስለሚወሰድ ቅጣቱን ይበልጥ ሊያባብሰው ይችላል።

🚫 2. ሊወሰዱ የሚችሉ ሌሎች ከባድ እርምጃዎች፦

  • 🔹 የማሽኑ መዘጋት (Block መሆን)፦ ማሽኑ በወቅቱ ካልታደሰ ከገቢዎች ሲስተም ጋር ያለው ትስስር በራሱ ጊዜ ሊዘጋ (Block ሊሆን) ይችላል። ይህ ከሆነ ደግሞ ደረሰኝ መቁረጥ ስለማይችሉ ንግድዎ ላይ ቀጥተኛ መስተጓጎል ይፈጥራል።
  • 🔹 ደረሰኝ አለመስጠት በሚል መታየት፦ ማሽኑ ባለመታደሱ ምክንያት ደረሰኝ ሳይቆርጡ ለደንበኛ ሽያጭ ካከናወኑ፣ ድርጊቱ እንደ "ደረሰኝ አለመስጠት" ተቆጥሮ የብር 25,000 ተጨማሪ ቅጣት እና የወንጀል ክስ ሊያስከትል ይችላል።

💡 ማጠቃለያ ምክር፦ በቅጣትና በማሽን መዘጋት ምክንያት ስራዎ እንዳይስተጓጎል ሁልጊዜ የማሽንዎ የማደሻ ጊዜ ከመድረሱ በፊት ለፈቃድ ሰጪው አካል በማቅረብ ማሳደስዎን ያረጋግጡ!

መረጃው ለሌሎች ነጋዴዎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

የዊዝሆልዲንግ ታክስ አሰላል

📊 የ3% ዊዝሆልዲንግ ታክስ አሰላል ደንብ

ተቀናሽ የሚደረገው 3% ዊዝሆልዲንግ ታክስ በቪኤቲ (VAT) ላይ ይታሰባልን?

ተቀናሽ የሚደረገው ሦስት በመቶ ዊዝሆልዲንግ ታክስ የሚሰላበት የእቃ ወይም የአገልግሎት የክፍያ መጠን የተጨማሪ እሴት ታክሱን ይጨምራል ወይስ አይጨምርም? እንዴት ነው የሚሰላው?

ዝርዝር መመሪያውንና ምሳሌውን እዚህ ያንብቡ 📖

⚠️ ዋናው ደንብ፦

አይጨመርም! 3% የዊዝሆልዲንግ ታክስ (Withholding Tax) የሚሰላው የተጨማሪ እሴት ታክስን (VAT) ሳይጨምር በዕቃው ወይም በአገልግሎቱ ዋና ዋጋ ላይ ብቻ ነው።

የክፍያ ሰነድ (ኢንቮይስ) መሠረታዊ ክፍሎች፦

  • 🔹 የዕቃው ወይም አገልግሎቱ ዋና ዋጋ፦ ይህ 3% ዊዝሆልዲንግ ታክስ የሚሰላበት መነሻ ሂሳብ ነው።
  • 🔹 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT)፦ በዋናው ዋጋ ላይ ብቻ ተሰልቶ የሚቀመጥ።
  • 🔹 የሁለቱ ድምር፦ ጠቅላላ የኢንቮይስ ዋጋ።

🧮 ተግባራዊ ምሳሌ፦

አንድ ድርጅት የብር 10,000 ዕቃ ወይም አገልግሎት ቢገዛ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% ቢሆን፦

• የዕቃው/አገልግሎቱ ዋና ዋጋ፦ ብር 10,000

• ተጨማሪ እሴት ታክስ (15% VAT)፦ ብር 1,500

• ጠቅላላ የክፍያ ሰነድ (ኢንቮይስ) ድምር፦ ብር 11,500


📌 የዊዝሆልዲንግ ታክስ አሰላል፦
3% ዊዝሆልዲንግ የሚሰላው በዋናው ዋጋ (ብር 10,000) ላይ ብቻ ስለሆነ፦
Withholding Tax = 10,000 × 3% = ብር 300


💰 ለአቅራቢው የሚከፈለው ጠቅላላ የተጣራ ሂሳብ፦
ስለዚህ ዊዝሆልዲንግ ታክስ በሚቀነስበት ጊዜ የቪኤቲ (VAT) ሂሳቡ መደመር የለበትም። ክፍያ ፈጻሚው አካል ለባለአገልግሎቱ/ለአቅራቢው የሚከፍለው ጠቅላላ ሂሳብ፡
ጠቅላላ ድምር (ብር 11,500) - ዊዝሆልዲንግ ታክስ (ብር 300) = ብር 11,200 ይሆናል ማለት ነው።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

🚫 ያለ አስመጪነት ንግድ ፈቃድ ዕቃ ማምጣት ይቻላል?

ስለ ግል መገልገያና የንግድ ዕቃዎች ግልጽ መረጃ

ብዙዎች ዕቃዎችን ያለ አስመጪነት ንግድ ፈቃድ ለአንድ ጊዜ ብቻ ማምጣት እንደሚቻል ያስባሉ፤ ነገር ግን ሕጉ የሚለው የሚከተለውን ነው፦

ዝርዝር መመሪያውን እዚህ ያንብቡ 📖

⚠️ ዋናው ደንብ፦

ያለ ንግድ ፈቃድ ማንኛውንም ዕቃ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት አይቻልም

ከዚህ ደንብ ውጭ የሚስተናገዱ (ልዩ ሁኔታዎች)፦

  • 🔹 የንግድ ባህሪ የሌላቸው ዕቃዎች፦ በስጦታ መልክ የሚላኩ ዕቃዎች።
  • 🔹 ለመንገደኞች፦ መንገደኞች ይዘዋቸው የሚገቡ የግል መገልገያዎች።
  • 🔹 ለተመላሽ ኢትዮጵያውያን፦ በገንዘብ ሚኒስቴር የግል መገልገያ መመሪያ ዝርዝር ላይ የተቀመጡ ዕቃዎች።

ማጠቃለያ፦ በመመሪያው ላይ ከሰፈሩት "የግል መገልገያ" ዕቃዎች ውጭ ማንኛውም አይነት ዕቃ ለማስገባት የአስመጪ የንግድ ፈቃድ መኖሩ ግዴታ ነው!

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

💰 የዕቃዎች ቀረጥና ታክስ አወሳሰን (CIF Value)

ዕቃዎች ወደ ሀገር ሲገቡ ቀረጥ እንዴት ይሰላል?

የዕቃዎች ቀረጥና ታክስ የሚወሰነው በዕቃው አጠቃላይ የCIF ዋጋ እና በዕቃው የታሪፍ ምጣኔ ላይ ተመስርቶ ነው፡:

የCIF ዝርዝር እና አሰላስል እዚህ ያንብቡ 📖

CIF ማለት ምን ማለት ነው?

CIF (Cost, Insurance, and Freight) ማለት የሚከተሉት ወጪዎች ድምር ውጤት ነው፦

  • 🔹 C (Cost)፦ የዕቃው መግዣ ዋጋ።
  • 🔹 I (Insurance)፦ የኢንሹራንስ ወይም የመድን ዋስትና ወጪ።
  • 🔹 F (Freight)፦ የማጓጓዣ ወይም የጭነት ዋጋ።
  • 🔹 ሌሎች ወጪዎች፦ ከዕቃው ጋር ተያያዥ የሆኑ ሌሎች አስፈላጊ ወጪዎች።

ቀመር (Formula)

CIF = የመግዣ ዋጋ + ኢንሹራንስ + ማጓጓዣ

ቀረጥ የሚወሰንባቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

  • 👉 የታሪፍ ምጣኔ፦ እንደ ዕቃው ዓይነት (ለምሳሌ የቤት ዕቃ፣ የኢንዱስትሪ መሣሪያ፣ አልባሳት) የሚቀመጥ የመቶኛ ስሌት ነው።
  • 👉 የምንዛሬ ተመን፦ ስሌቱ የሚሠራው ዕቃው ጉምሩክ በደረሰበት ቀን ባለው የውጭ ምንዛሬ ተመን ወደ ብር ተቀይሮ ነው።

ማስታወሻ፦ ትክክለኛውን የCIF ዋጋ ማሳወቅ ከቅጣት ነፃ ያደርጋል፤ የጉምሩክ ሂደቱንም ያፋጥነዋል።

ለተጨማሪ መረጃ ብሎጋችንን ይከታተሉ! 💡

🚢 ለአስመጪና ላኪዎች፦ ለጉምሩክ መቅረብ ያለባቸው ሰነዶች

የጉምሩክ ስነ-ስርዓትን ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ መረጃዎች

በፅሁፍ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የእቃ ዲክላራሲዮን ለጉምሩክ ሲቀርብ የሚከተሉት ሰነዶች ተሟልተው መቅረብ ይኖርባቸዋል፦

የሰነዶቹን ዝርዝር እዚህ ያንብቡ 📖
  • የታደሰ የንግድ ፍቃድ፦ በዘመኑ የታደሰና ለስራው ብቁ መሆኑን የሚያረጋግጥ።
  • የማጓጓዣ ሰነዶች (Shipping Documents)፦ ዕቃው የተጫነበትን መንገድና ሁኔታ የሚያሳዩ።
  • የዋጋና የዕቃ ዝርዝር መግለጫ (Invoice & Packing List)፦ የዕቃው አይነት፣ ብዛትና ጠቅላላ ዋጋ በዝርዝር የያዘ።
  • የባንክ ፍቃድ (Bank Permit)፦ ከባንክ የተገኘ የክፍያ ወይም የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ።
  • የስሪት ሀገር ማረጋገጫ (Certificate of Origin)፦ ዕቃው የት ሀገር እንደተመረተ የሚያሳይ ምስክር ወረቀት።
  • ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች፦ በመመሪያ የሚወሰኑና እንደ ዕቃው አይነት የሚጠየቁ ተጨማሪ ሰነዶች።

💡 ማሳሰቢያ፦

እነዚህ ሰነዶች ተሟልተው መቅረባቸው የጉምሩክ ሂደቱን ፈጣን ከማድረጉም በላይ አላስፈላጊ መዘግየቶችን ያስቀራል።

መረጃው ለሚመለከታቸው እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

⚖️ ታክስን አሳንሶ ማሳወቅ የሚያስከትለው ቅጣት

መረጃው ለታክስ ከፋዮች ሁሉ ይድረስ!

በታክስ ማስታወቂያ የተገለጸው የታክስ መጠን ታክስ ከፋዩ ሊከፍል ከሚገባው ትክክለኛ የታክስ መጠን ያነሰ ሆኖ ከተገኘ (የታክስ ጉድለት) የሚከተሉት ቅጣቶች ይጣላሉ፦

የቅጣቱን ደረጃዎች እዚህ ያንብቡ 📖

1. ለመጀመሪያ ጊዜ ጥፋት፦

በታክስ ጉድለቱ መጠን ላይ 10% (አሥር በመቶ) ቅጣት ይከፈላል።

2. ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋት፦

ጥፋቱ ለሁለተኛ ጊዜ ሲደገም የቅጣቱ መጠን ወደ 30% (ሰላሳ በመቶ) ከፍ ይላል።

3. ለሦስተኛ ጊዜ እና ከዚያ በላይ፦

ጥፋቱ ለሦስተኛ ጊዜና ከዚያ በላይ ሲደገም የቅጣቱ መጠን ወደ 40% (አርባ በመቶ) ከፍ ይላል።

📢 ማወቅ ያለብዎት ተጨማሪ ነጥቦች፦

  • 👉 ምክንያታዊ አቋም፦ ጉድለቱ የተፈጠረው ሚኒስቴሩ ማብራሪያ ባልሰጠበት አከራካሪ ሕግ ላይ በተወሰደ ምክንያታዊ አቋም ከሆነ ቅጣቱ ተፈጻሚ አይሆንም።
  • 👉 የጥፋት ብዛት አቆጣጠር፦ የጥፋቱ መጠን የሚቆጠረው አዋጁ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለየታክስ ዓይነቱ ተለይቶ እና ጥፋት በተገኘባቸው የታክስ ማስታወቂያዎች ብዛት ነው።

ትክክለኛ መረጃን በማቅረብ ከከባድ የገንዘብ ቅጣት ይዳኑ!

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

አክሲዮን ትርፍ ድርሻ (Dividend) የታክስ መመሪያ

አንድ ትርፍ ያገኘ ድርጀት ሁለት መርጫ አለው ካፒታል ማሳደግ ወይም የትርፍ ድርሻ ግብር መክፈል


1. የግብር መጠን፦

ማንኛውም የትርፍ ድርሻ ያገኘ ሰው (ነዋሪም ሆነ ነዋሪ ያልሆነ) በገቢው ላይ 15% የገቢ ግብር የመክፈል ግዴታ አለበት።

2. ግብሩ መቼ መከፈል አለበት?

የትርፍ ድርሻ ግብር የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በ 14 ወራት ውስጥ መከፈል አለበት።

3. ካፒታል ማሳደግ (ታክስ ላለመክፈል)፦

ትርፉን ለባለቤቱ ከመስጠት ይልቅ ካፒታል ለማሳደግ ከተፈለገ፣ ዓመቱ ባለቀ በ 12 ወራት ውስጥ ካፒታሉ ማደግ አለበት።

ካፒታል አደገ የሚባለው፦ በውልና ማስረጃ የጸደቀ ቃለ-ጉባኤ ሲኖር፣ በ e-trade ካፒታሉ ሲሻሻል እና ሰነዶቹ ለገቢዎች ቀርበው ከፋይሉ ጋር ሲያያዙ ነው።

4. በጊዜው ካልተከፈለ የሚመጣ ቅጣት፦

ትርፉ ሳይከፈል ወይም ካፒታል ሳይሳደግ ቢቀር የፍሬ ግብር፣ የወለድ እና የአስተዳደር መቀጫ ይጣልባቸዋል።


ድርጅቱ የትርፍ ድርሻ መከፈል የሚጠበቅበት ትርፍ ካገኘ ብቻ ነው
ታክስ ከመወሰኑ በፊት ከታወቀ፦ የ 10,000 ብር መቀጫ ብቻ።

ታክስ ከተወሰነ በኋላ ከሆነ፦ ከፍሬ ግብሩ በተጨማሪ ከ 5% እስከ 25% የሚደርስ ቅጣት ይጣልበታል።

⚠️ ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት

ለታክስ ከፋዮች የቀረበ ማሳሰቢያ

ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ መክፈያ ጊዜው ውስጥ ታክስ ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ የሚከተሉት የገንዘብ ቅጣቶች ይጣሉበታል፦

የቅጣቱን ዝርዝር መመሪያ እዚህ ያንብቡ 📖

ሀ) ለመጀመሪያው ወር፦

ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ) ቅጣት ይከፈላል።

ለ) ለቀጣይ ወራት፦

ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ ተጨማሪ 2% (ሁለት በመቶ) ቅጣት ይታሰባል።

📌 ዋና ዋና ደንቦች፦

  • 👉 የሚጣለው የቅጣት መጠን ከዋናው የታክስ ዕዳ መብለጥ የለበትም።
  • 👉 መከፈል በማይገባው ታክስ ላይ ሳይከፈል በዘገየበት የተጣለ ቅጣት ለታክስ ከፋዩ ይመለሳል።
  • 👉 ይህ ቅጣት ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ ከሚከፈል ታክስ ጋር በተገናኘ በሚጣል ቅጣት ላይ ተፈጻሚ አይሆንም።

ታክስን በጊዜ በመክፈል ከትርፍ ወጪ ራስዎን ይጠብቁ!

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

🧾 የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ (Purchase Voucher) አጠቃቀም

ለግብር ከፋዮች የቀረበ ጠቃሚ መረጃ

የሂሳብ መዝገብ የሚይዝ ታክስ ከፋይ የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ከሌለባቸው ታክስ ከፋዮች ጋር ለሚያደርገው ግብይት ከታክስ ባለስልጣኑ በማስፈቀድ የወጭ ማስረጃ የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ (Purchase Voucher) አሳትሞ መጠቀም ይችላል።

ስለ Purchase Voucher ዝርዝር መረጃ እዚህ ያንብቡ 📖

Purchase Voucher (የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ) ምንድነው?

"ገዥው ራሱ አዘጋጅቶ ሽያጭን የሚያስፈርምበት ደረሰኝ" ማለት ነው። ሻጩ ደረሰኝ የሌለው ግለሰብ ሲሆን፣ ገዥው ድርጅት ያወጣውን ወጪ ለታክስ ባለሥልጣን ለማስረዳት ይጠቀምበታል።

1. ለምን ያገለግላል?

  • 👉 ለወጪ ማረጋገጫ፦ ወጪው በኦዲት ጊዜ ተቀባይነት እንዲኖረውና ከገቢ ላይ ተቀንሶ ትክክለኛው ግብር እንዲታሰብ ይረዳል።
  • 👉 ለሕጋዊነት፦ ደረሰኝ ከማይሰጡ ሰዎች ጋር የተደረገን ግብይት ሕጋዊ መልክ ያስይዛል።

2. በደረሰኙ ላይ ምን መያዝ አለበት?

  • የሻጩ ሙሉ ስም፣ አድራሻ እና TIN (ካለው)
  • የተገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ዝርዝር
  • የግብይቱ ጠቅላላ ዋጋ እና የተፈጸመበት ቀን
  • የሻጩ ፊርማ (በጣም ወሳኝ ነው)

3. የት ይታተማል?

ከገቢዎች ባለሥልጣን ፈቃድ በማግኘት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት አሳትሞ መጠቀም ይቻላል።

✅ መጠቀም የተፈቀደላቸው ዋና ዋና ግዢዎች፦

  • ከገበሬዎች የሚገዛ እንስሳ፣ እህል፣ አትክልትና ፍራፍሬ
  • ለኮንስትራክሽን የሚሆኑ ድንጋይ፣ አሸዋ፣ ኖራና እንጨት
  • በሰው ጉልበት የሚሰራ የጫኝና አውራጅ አገልግሎት
  • ያገለገሉ/የወዳደቁ ዕቃዎች ግዢ
  • ተሸከርካሪ ኪራይ እና ለማገዶ የሚሆን ከሰልና እንጨት

መረጃው ለነጋዴው ማህበረሰብ እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📜 የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የሕትመት መመሪያ

አሳትሞ የሕትመት አገልግሎት ለማግኘት ማሟላት የሚገቡ ቅደመ ሁኔታዎች

ማንኛውንም የሕትመት ሥራ (በተለይም ደረሰኞችንና ሕጋዊ ሰነዶችን) ለማሳተም የሚከተሉትን መመሪያዎች መከተል ግዴታ ነው፦

ሙሉውን ዝርዝር መመሪያ እዚህ ያንብቡ 📖

1. ሕጋዊ ሰነዶች (Legal Requirements)

  • • የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ማቅረብ።
  • • ልዩ ፈቃድ ለሚፈልጉ ሕትመቶች (ለምሳሌ፦ ደረሰኝ) ከሚመለከተው የመንግሥት መሥሪያ ቤት የተሰጠ የፈቃድ ደብዳቤ ማያያዝ።

2. የመረጃ ትክክለኛነት (Accuracy)

  • • ሊታተም የሚፈለገው መረጃ (ጽሑፍ፣ ዲዛይን፣ ፎቶ) ትክክል መሆኑን ደንበኛው በፊርማው ማረጋገጥ ይኖርበታል።
  • • መረጃው በሶፍት ኮፒ (በፍላሽ ወይም በሲዲ) በጥራት ተዘጋጅቶ መቅረብ አለበት።

3. ክፍያና ስምምነት (Payment & Contract)

• እንደ ሥራው ዓይነት የቅድሚያ ክፍያ መፈጸም ወይም በድርጅቶች መካከል የሚደረግ የውል ስምምነት (የእምነት ደብዳቤ) መፈረም ያስፈልጋል።

4. የናሙና ማረጋገጫ (Sample Approval)

• ሕትመቱ ከመጀመሩ በፊት የሚቀርበውን ናሙና (Proof) አይቶ ማጽደቅ የደንበኛው ኃላፊነት ነው። ናሙናውን ለማጽደቅ የሚወሰደው ጊዜ በሥራው ማጠናቀቂያ ጊዜ ላይ እንደማይታሰብ መገንዘብ ያስፈልጋል።

5. ርክክብ (Delivery)

• ሥራው ተጠናቆ ሲገለጽ በወቅቱ መረከብና ቀሪ ክፍያዎችን መክፈል።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

☀️ በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግዙፍ የሶላር እና የጋዝ ፋብሪካዎች ተመረቁ

📅 ሚያዚያ 2018 ዓ.ም

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የተመረቁት እነዚህ ፋብሪካዎች፣ የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ናቸው።

የፋብሪካዎቹን ዝርዝር የማምረት አቅም እዚህ ያንብቡ 📖

🔋 የሶላር ፋብሪካዎች (ቶዮ ሶላር፣ ኦሪጂን እና ሉሚንቴክ)፦

  • በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው።

💨 የኤች.ዜድ (HZ) ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካ፦

በዓመት ለገበያ የሚያቀርባቸው ምርቶች፦

  • 900 ቶን ኦክስጅን
  • 40,000 ቶን ናይትሮጅን
  • 7 ቶን ሃይድሮጅን

"ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የኢነርጂ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የማይበገር ሁለንተናዊ እድገትን ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ነው" — የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት

ለሀገራችን ብስራት የሆነውን መረጃ ሼር ያድርጉ! 🇪🇹

📢 ታላቅ ብስራት ለባለሀብቶች፡ በነፃ የንግድ ቀጠና የግብር ነፃ መብት ተፈቀደ

📅 ሚያዚያ 2018 ዓ.ም (የገቢዎች እና የገንዘብ ሚኒስቴር)

መንግስት የሀገሪቱን የኢንዱስትሪ ልማት ለማፋጠን እና የግብዓት አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ በነፃ የንግድ ቀጠናዎች (Free Trade Zones) ውስጥ ለሚሳተፉ ባለሀብቶች ልዩ የታክስ ማበረታቻ ማድረጉን አስታውቋል።

ዝርዝር መረጃውን እዚህ ያንብቡ 📖

ለምን አስፈለገ?

የካፒታል እጥረት እና የግብዓት አቅርቦት ችግር የኢንዱስትሪ እድገታችንን እንዳያደናቅፉት አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ በካፒታላቸው ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማቃለል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

✅ ዋና ዋና ማበረታቻዎች፦

  • የግብር ነፃ መብት፦ በነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ ገብተው ዕቃዎችን ከውጭ በማስገባት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ ተወስኗል።
  • ቀረጥን አዘግይቶ መክፈል፦ ምርቶችን ሳይከፍሉ አስገብተው፣ ለገበያ በሚያቀርቡበት ወቅት ብቻ ቀረጥና ታክስ የሚከፍሉበት አሰራር ተዘርግቷል።
  • የካፒታል እፎይታ፦ ይህ አሰራር ባለሀብቶች ውስን የሆነውን ካፒታላቸውን ለስራ ማስፋፊያ እንዲጠቀሙበት ዕድል ይሰጣል።

የህግ መሠረት፦ ይህ ውሳኔ በገንዘብ ሚኒስቴር ደብዳቤ ቁጥር ታ500/ሃ/883/18 እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 586/2018 መሠረት ተፈጻሚ የሚሆን ይሆናል።

ባለሀብቶች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በነፃ የንግድ ቀጠናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ ተጋብዘዋል!

መረጃው ለሌሎች ባለሀብቶች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

⚖️ የሙያ ፈቃድ ያላቸው ባለሙያዎች እና አከራዮች የግብር አከፋፈል

📍 አዲስ የአሰራር መመሪያ

የንግድ ሥራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሙያ ፈቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ እና የቤት አከራዮችን በሚመለከት የወጣው መመሪያ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ይዟል፦

ዝርዝር መረጃውን ያንብቡ 📖

🔹 ጠበቆች እና የኢንሹራንስ ወኪሎች፦ ከዓመታዊ ገቢያቸው 35% እንደ ወጪ ተቀናሽ ተደርጎላቸው፣ በቀረው 65% ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብር ይከፍላሉ።

🔹 የመኖሪያ ቤት አከራዮች፦ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው አከራዮችም 35% እንደ ወጪ ተይዞላቸው፣ በቀረው 65% ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብር ይሰበሰባል።

🔹 የተሽከርካሪ ኪራይ (ኮድ 02 እና 03)፦ በተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችም አጠቃላይ የኪራይ ገቢያቸው በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ተሰልቶ ግብር እንዲከፍሉ ይደረጋል።

🔹 የከተማ ትራንስፖርት (ሜትር ታክሲዎችን ጨምሮ)፦ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ የሌለባቸው የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች፣ በደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብራቸው ተሰልቶ እንዲሰበሰብ ተወስኗል።

💡 ማስታወሻ፦

እነዚህ የግብር አከፋፈል ስሌቶች ለተከፋዮች ምቹ በሆነ መልኩ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት የሚከናወኑ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር ገልጿል።

መረጃው ለሚመለከታቸው እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📞 የታክስ እና የጉምሩክ ነፃ የጥሪ መስመር (8199)

📅 መጋቢት 05/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

በታክስ እና በጉምሩክ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እና መረጃ ማግኘት ለሚፈልጉ ግብር ከፋዮች በሙሉ የተዘረጋ ነፃ የጥሪ መስመር መኖሩን ያውቃሉ?

ስለ አገልግሎቱ ዝርዝር መረጃ 📖

የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ እና በጉምሩክ ጉዳዮች ላይ የተሟላ ማብራሪያ ለመስጠት በ 8199 ነፃ የጥሪ መስመር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

በዚህ መስመር ምን አይነት መረጃ ያገኛሉ?

  • 👉 ስለ አዳዲስ የታክስ አዋጆች ማብራሪያ
  • 👉 ስለ ጉምሩክ ስነ-ስርዓት ጥያቄዎች
  • 👉 ያጋጠሙዎትን የአሰራር ቅሬታዎች ለማቅረብ

የጥሪ ማዕከል፦ 8199

(ዘወትር በስራ ሰዓት ይደውሉ)

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

🚗 የተሽከርካሪዎች ዓመታዊ ግብርና የቴክኒክ ምርመራ (ቦሎ)

📍 ማወቅ ያለብን ዋና ዋና ነጥቦች

ተሽከርካሪ ያላቸው ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የቴክኒክ ምርመራ (ቦሎ) ለማድረግ የሚከተሉትን መረጃዎች መያዝ አለባቸው፦

ተጨማሪ ያንብቡ 📖

የታክስ ክሊራንስ፦ ለተሽከርካሪ ዓመታዊ ምዝገባና ምርመራ (ቦሎ) ለማድረግ የታክስ ከፋዩን ሂሳብ ኦዲት ማድረግ ሳያስፈልግ ክሊራንስ ይሰጣል።

የክፍያ ጊዜ፦ የተሽከርካሪ ዓመታዊ ግብር የሚከፈለው እንደ ሰሌዳው ቁጥር መጨረሻ ሆኖ፣ በየዓመቱ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መሆን አለበት።

አስፈላጊ ሰነዶች፦
• የታደሰ የንግድ ፈቃድ (ለንግድ ተሽከርካሪዎች)
• የሊብሬ ኮፒ
• የኢንሹራንስ (መድን) ዋስትና ሰነድ

ቅጣት፦ የጊዜ ገደቡ ካለፈ በኋላ ለሚከፈል ግብር እንደየ መዘግየቱ መጠን አስተዳደራዊ ቅጣቶችና ወለድ ሊታሰብ ይችላል።

💡 ጠቃሚ ምክር፦

የቦሎ ጊዜዎ ከመድረሱ በፊት የታክስ ክሊራንስዎን በ eTax ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ የገቢዎች ቅርንጫፍ በማውጣት እንግልትን ይቀንሱ።

መረጃው ለተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📊 በአዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት የገቢ ግብር ምጣኔ

📍 ሠንጠረዥ "መ" - ለሌሎች ገቢዎች የሚከፈል የታክስ መጠን

በአዲሱ የታክስ ማሻሻያ መሠረት ለተለያዩ የገቢ አይነቶች የተወሰነው የግብር ምጣኔ ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ተጨማሪ ያንብቡ 📖
የገቢ ዓይነት ነዋሪ ለሆኑ ነዋሪ ላልሆኑ
ለመድን አረቦን - 15%
ሮያሊቲ (Royalty) 10% 10%
በትርፍ ክፍፍል (Dividend) 15% 15%
በወለድ ገቢ 10% 10%
በስራ አመራር እና ቴክኒክ አገልግሎት 15% 15%
ከመዝናኛ አገልግሎት 15% -
የዕድል ሙከራ (ሎተሪ) 25% -
ሀብት በማስተላለፍ የሚገኝ ጥቅም - 15%

💡 ማስታወሻ፦

ይህ ሰንጠረዥ በዋናነት ነዋሪ ለሆኑ እና ላልሆኑ ግብር ከፋዮች የሚኖረውን ልዩነት በግልጽ ያሳያል።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📜 የቴምብር ቀረጥ አከፋፈል መመሪያ

📅 የካቲት 30/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀው የቴምብር ቀረጥ ስሌት እና ተመን ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ሙሉ የክፍያ ዝርዝሩን ይመልከቱ 📖
የሰነዱ ዓይነት የክፍያ ልክ
የመመስረቻ ጽሁፍ (አዲስ) ብር 350
የመመስረቻ ጽሁፍ (ማሻሻያ) ብር 100
ውል (Contract) ብር 5.00
የባለቤትነት ስም ማዛወር 2%
የኪራይ ውል 0.5%
የውክልና ስልጣን ብር 35.00
የቅጥር ውል 1% (ከአንድ ወር ደመወዝ)

💡 ማሳሰቢያ፦

ሌሎች ዝርዝር ሰነዶች እንደ ዋጋቸው (Ad Valorem) 1% ወይም እንደ ብዛታቸው (Fixed) ተሰልተው የሚከፈሉ ይሆናል።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📢 ለደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች፦ የትርፍ ግብር ቅድመ ክፍያ (Advance Payment)

📍 የ2018 በጀት ዓመት መረጃ

የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የንግድ ትርፍ ግብር ቅድመ ክፍያን በተመለከተ ማወቅ ያለብን 8 ወሳኝ ነጥቦች፦

ተጨማሪ ያንብቡ 📖

1. የሂሳብ መዝገብ፦ መዝገብ ማቅረብ አያስፈልግም። የምንከፍለው በ2017 ዓ.ም ከከፈልነው ግብር 25% (1/4) ብቻ ነው።

2. አዲስ ነጋዴዎች፦ በ2018 ዓ.ም ስራ የጀመሩትን አይመለከትም

3. የ3% ግብር (Withholding)፦ በመስከረም ወር የተቀነሰባችሁ የ3% ግብር ከሚጠበቅባችሁ 25% በላይ ከሆነ፣ ትርፉ ወደ ቀጣዩ ሩብ ዓመት ይዞርላችኋል።

4. የቅድመ ክፍያው መጨረሻ፦ በየሩብ ዓመቱ የከፈላችሁት ድምር በ2019 ዓ.ም ከሚከፈለው ጠቅላላ ግብር ላይ ተቀናሽ ይደረጋል።

5. የክፍያ ጊዜ፦ ከመጀመሪያው ሩብ ዓመት ጀምሮ ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ተከፍሎ ማለቅ አለበት።

6. ተቀናሽ የሚሆን Withholding፦ ከሐምሌ 1 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም የተቀነሰባችሁ 3% ብቻ ተቀናሽ ይሆናል።

7. "0" (ዜሮ) ሪፖርት ላደረጋችሁ፦ ባለፈው ዓመት ዜሮ ላሳወቃችሁ፣ በግምት ከዓመታዊ ገቢያችሁ 2.5% እንድትከፍሉ ይደረጋል።

8. የክፍያ መንገድ (eTax)፦ በ "Taxpayer Services" ሜኑ ውስጥ "Advance Quarterly Payment Advice - Schedule C" የሚለውን በመጫን ኦንላይን ማሳወቅ ይቻላል።

⚠️ ማሳሰቢያ፦

ግብርን በወቅቱ በማሳወቅና በመክፈል ካልተፈላጊ ቅጣትና ወለድ ራስዎን ይጠብቁ።

መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

📋 የታክስ ክሊራንስ ለመስጠት ኦዲት የማያስፈልጋቸው አገልግሎቶች

📅 ጥር 03/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሠረት፣ ለሚከተሉት አገልግሎቶች ታክስ ከፋዩን ኦዲት ማድረግ ሳያስፈልግ የታክስ ክሊራንስ ሊሰጥ ይችላል፦

ተጨማሪ ያንብቡ 📖
  • 👉 የንግድ ሥራ ወይም የሙያ ፈቃድ ለማደስ፤
  • 👉 በጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፤
  • 👉 ለተሽከርካሪዎች ወይም ለኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ዓመታዊ ምርመራ (ቦሎ) ለማድረግ፤
  • 👉 የባንክ ብድር ለማግኘት፤
  • 👉 የመድን ካሳ ለማግኘትና የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ለማድረግ፤
  • 👉 የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፤
  • 👉 የንግድ ዘርፍ ቅነሳ ለማድረግ (የንግድ ሀብት መቀነስን ሳይጨምር)፤
  • 👉 ድርጅቶች ሲዋሀዱ የታክስ ዕዳን አካቶ ለመቀጠል ለሚቀርብ የፀደቀ ሰነድ፤
  • 👉 የጡረታ መዋጮ ስለመከፈሉ ማረጋገጫ ለማግኘት።

💡 ማስታወሻ፦

እነዚህ አገልግሎቶች የታክስ ከፋዩን ጊዜና ወጪ በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋሉ።

መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡

⚖️ ከታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ጋር የተገናኙ ወንጀሎች

📍 የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008

የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም በህግ ያስቀጣል፦

  • ከአንድ በላይ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር መውሰድ ወይም ለመውሰድ መሞከር።
  • የራስን መለያ ቁጥር (TIN) ሌላ ሰው እንዲጠቀምበት መስጠት።
  • የሌላን ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር መጠቀም።

⚠️ ቅጣቱ፦

💰 20,000 (ሃያ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት እና

⛓️ ከ 1 ዓመት እስከ 3 ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራት ያስቀጣል።

ተጨማሪ ያንብቡ 📖

🔹 ስለ ብዛቱ፦ ከአንድ በላይ ቁጥር ለመውሰድ ከተሞከረ፣ ቅጣቱ ለእያንዳንዱ ቁጥር በተናጠል ተፈጻሚ ይሆናል።

🔹 ልዩ ሁኔታ፦ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩ ባለቤት ለታክስ ወኪሉ (Tax Agent) በጽሁፍ ፈቅዶ ወኪሉ ለባለቤቱ ጉዳይ ብቻ ከተጠቀመበት ቅጣቱ ተፈጻሚ አይሆንም።

ምንጭ፦ በበኃይሉ ሺመልስ | መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! 💡